በጎፋ ዞን በአራት ወረዳዎች የውሃ መሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚያግዝ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
የውሃ መሠረተ ልማት አስተዳደርንና የምግብ ዋስትናን የሚያሻሽሉ ፈጠራዎች ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ ።
ሰኔ/12/2018 ዓ.ም
''ስማርት ዋሽ '' የተሰኘ በኢትጵያ የዉሃ መሠረተ ልማት አስተዳደርንና የምግብ ዋስትናን የሚያሻሽሉ ፈጠራዎች ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል ።
የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ፣ ፕሮጀክቱ የውሃ መሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት እየሰራ ያለውን ተግባር አድንቀዋል ።
ፕሮጀክቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመረጧቸው አራት ወረዳዎች በጎፋ ዞን እንደሚገኙ ጠቅሰዋል ።
ፕሮጀክቱ የመጠጥና የመስኖ ዉሃ አገልግሎችን በማዘመን ለህብረተሰቡ ኑሮ መሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል ።
የዞኑ መንግስትም አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ከድርጅቱ ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አስረድተዋል ።
የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝዳንት ተክሉ ወጋየሁ(ዶ/ር)፣ ዩኒቨርስቲው በበጎ ተግባራት ከተማሰሩ ድርጅቶች ጋር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል ።
''ስማርት ዋሽ'' የውሃ ግብዓቶችን ለማዘመንና በምግብ ራስን ለመቻል የሚያግዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል ።
ዩኒቨርስቲው ከፕሮጀክቱ ጋር በመተባበር በውሃ አጠባበቅና አጠቃቀም ዙሪያ ለማህበረሰቡ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን የእሰራ መሆኑን አብራርተዋል ።
ድርጅቱ የሚያከናወናቸው ተግባራት የውሃ ንፅህናን በማስጠበቅና የመስኖ ውሃ አጠቃቀምን በማዘመን የማህበረሰቡን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚረዳ አስረድተዋል ።
በዩኒቨርሲቲው የዉሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፍክ ዳይሬክተር ኢ/ር ታምሩ ተሰሜ (ዶ/ር)፣ዩኒቨርስቲው ለስራው መዘመን የሚረዱ በቴክኖሎጂ የታገዙ ስልጠናዎችን በመስጠት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል ።
በጎፋ ዞን በአራት ወረዳዎች የውሃ መሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚያግዝ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።