በጎፋ ዞን በደምባ ጎፋ ወረዳ በዛንጋ አዋንዴ ቀበሌ በበንዲ ተፋሰሰ በሰዎች ለሰዎች ግብረ-ሰናይ ድርጅት የተራቆቱ ተራሮችን የማልማት ችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት ስራ ምልከታ ተደረገ።
ሣውላ፦ሰኔ 22/2018 ዓ/ም
የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቦረና ቦላዶ የተመራው የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በደምባ ጎፋ ወረዳ በዛንጋ አዋንዴ ቀበሌ በበንዲ ተፋሰሰ በሰዎች ለሰዎች ግብረ-ሰናይ ድርጅት የተራቆቱ ተራሮች የማልማት ችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት ስራ ምልከታ በጋራ አድርገዋል።
የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቦረና ቦላዶ እንደተናገሩት እንደ ሀገር ካርበን እጅጉን እየጨመረ በመምጣቱ በየአካባቢው የተፈጥሮ አደጋዎች እየተከሰቱ ይገኛል ብለው እኛም የዚህ ችግር ተጎጂዎች ነን ብለዋል።
አያይዘውም በዛንጋ አዋንዴ ቀበሌ በበንዲ ተፋሰስ በሰዎች ለሰዎች ግብረ-ሰናይ ድርጅት አንድ ተራራ የማልማት ስራ የተጀመረው ድርጅቱ ማህበረሰቡ በተፋሰሰ በተለየው ተራራ ላይ ችግኞችን በመትከል በማልማት ከሚገኘው የኦክስጂን አየር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይደረጋል በማለት ተናግረዋል።
በተጨማሪም ተራሮችን የማልበስ ስራ በዚህ ቀበሌ ብቻ የሚሰራ እንዳልሆነ ተናግረው በሁሉም የዞኑ መዋቅሮች ማህበረሰቡን በማሳተፍ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የጎፋ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ደግፌ በበኩላቸው እንደተናገሩት የግብርና ስራ ዘርፈ ብዙ ቢሆንም የመጀመሪያው አካባቢን ማልማትና ተራሮችን በደን መሸፈነ እንደሆነ ገልፀዋል።
አክለውም እንደ ዞን 27 ሺህ ሄክታር ለማልማት በማቀድ እየተሰራ እንዳለ ተናግረው በረጂና በማህበረሰብ ተሳትፎ ትልልቅ ተራራ ልማቶች የችግኝ ተከላዎች በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ይተገበራል ብለዋል።
ፕሮጀክት አስተዳዳሪ አቶ በረከት ጋሻበዛ የካርበን ልቀት ለመቀነስ ሰዎች ለሰዎች ፕሮጀክት በአካባቢ እየተፈጠረ ያለውን የተራራ መራቆት እንዲሁም የወደፊት ስጋትን ለመከላከል ከረጂ ድርጅቶች በኩል ሰፊ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የደምባ ጎፋ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አራሹ አበበ እንደተናገሩት በማህበረሰብ የነቃ ተሳትፎ የተራቆቱ መሬቶችን እና አለግባብ ተጨፍጭፈው ገላጣ የሆኑ ተራሮችን በችግኝ ተከላ በማካለል እንዲሁም በችግኝ በመሸፈን እና በመንከባከብ ከእንሰሳትና ከሰው በመጠበቅ እንደሚለማ ተናግረዋል።
አንዳንድ ያነጋገርናቸው የአካባቢ ነዋሪዎች ሰዎች ለሰዎች ድርጅት በቀበሌው በመግባቱ ተደስተው የማህበረሰብ ተሳትፎ ላይ በንቃት እንሳተፋለን በማለት ተናግረዋል።
በጎፋ ዞን በደምባ ጎፋ ወረዳ በዛንጋ አዋንዴ ቀበሌ በበንዲ ተፋሰሰ በሰዎች ለሰዎች ግብረ-ሰናይ ድርጅት የተራቆቱ ተራሮችን የማልማት ችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት ስራ ምልከታ ተደረገ።